የ17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ተከበር

ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በሁሉም የሀገራችን ክፍሎችሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታበሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡ 

ቀኑ በድርጅቱ ሲከበር የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽታሁን ዋለ የማኔጅመንት አባላትና ከየስራ ክፍሉ የተውጣጡ ሰራተኞች በበዓሉ ላይ ታድመዋል፡፡

የሰንደቅ ዓላማ መስቀል ስነ-ስርዓቱን የፌዴራል ፖሊስ አባላት በወታደራዊ ሰልፍ ያደመቁት ሲሆን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽታሁን ዋለ ሰንደቅ ዓላማውን በመስቀል ቀኑን አክብረዋል፡፡